BRIGHT FUTURE FOR ETHIOPIANS !!!

BRIGHT FUTURE FOR ETHIOPIANS !!!

Tuesday, 5 November 2013

የኢትዮጵያ ህዝብ ለመለስ ፋውንዴሽን ጆሮዉንም አይኑንም አንደነፈገ ታወቀ


የህወሀት መስራችና የረጂም ግዜ መሪ የነበረዉ ዘረኛዉ መለስ ዜናዊ ከዚህ አለም በሞት በተለየ በስምንት ወሩ ባለፈዉ መጋቢት መጨረሻ ላይ ይፋ ሆኖ የተመሰረተዉ የመለስ ፋውንዴሽን ከህዝብ ያገኛል ተብሎ የተገመተዉን የገንዘብ መዋጮ የሩቡን ግማሽም አለማግኘቱን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ከዝግጅት ክፍላችን ጋር በሰልክ ባደረጉት ቃለ ምልልስ ገለጹ፡፡ በመለስ ፋውንዴሽን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 781/2005 መንግስታዊ ተቋም ሆኖ የተመሰረተው ይህው ፋውንዴሽን ቤተመጻህፍትና ሙዚየም ለማቋቋም በማሰብ ሕዝቡ ገንዘብ እንዲያዋጣ በየቀኑ በመንግስት መገናኛ ብዙሃን ቅስቀሳ ከተጀመረ ከአምስት ወራት በላይ ቢቆጠርም እየተዋጣ ያለው ገንዘብ እጅግ አነስተኛ መሆኑ ታውቋል፡፡

ህዝብ በያለበት ለመለስ ፋዉንዴሺን የገንዘብ መዋጮ ለማድረግ ፈቃደኛ ያልሆነዉ ፋውንዴሽኑን በበላይነት የምትመራዉና የሙስናዋ እመቤት በመባል የምታወቀዉ አዜብ መስፍንና ሟቹ ባለቤቷ ከህዘብ ዘርፈዉ በውጪ አገር ባንኮች ከፍተኛ ገንዘብ ማከማቸታቸዉን ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃንና በውጪ አገር የሚገኙ የኢትዮጽያ መገናኛ ብዙኋን በተደጋጋሚ በመዘገባቸዉ እንደሆን ብዙዎች በመናገር ላይ ናቸዉ። ከዚህ በተጨማሪ አብዛኛው የመንግስት ሰራተኛና የግሉ ዘርፍ ለህዳሴዉ ግድብ ገንዘብ እያዋጡ መሆናቸዉና ህዝቡ መለስ ዜናዊን ለመሰለ ሃያ አንድ አመት ሙሉ ለረገጠዉ ጨቋኝና ከፋፋይ ሰዉ የገንዘብ መዋጮ ማድረግ ባለመፈለጉ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። የአዲሰ አበባ ምንጫችን ጨምሮም እንደገለጸዉ መዋጮው በውዴታ በባንክ ገቢ የሚደረግና ለጋሹ ስሙን ከማስመዝገብ በላይ መስጠትና አለመስጠቱ የማይታወቅ በመሆኑ ከፍተኛ የግንባሩ ካድሬዎችና ራሳቸውን የኢህአዴግ ደጋፊ ባለሃብቶች ነን የሚሉት ሳይቀሩ ለመዋጮው እጃቸውን አለመዘርጋታቸው መረጃው ያሳያል።

G7 November 2, 2013

የወያኔ ፍትሻ ባህርዳርንና ኗሪዎቿን አማረረ


የዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ ካድሬዎች፤ ፖሊሶችና የጸጥታ ሀይሎች ለግዜዉ ምክንያቱ ባልታወቀ ምክንያት በባህርዳር ከተማ ዉስጥ ከፍተኛ ፍተሻ እያካሄዱ መሆኑን ባህርዳር ዉስጥ የሚገኙ የግንቦት ሳበት ድምጽ ዘጋቢዎች በስልከ በላኩልን ዜና ገለጹ። በተላይ ከሳምንቱ መግቢያ እስከ ሳምንቱ አጋማሽ በነበረዉ ግዜ ዉስጥ በከተማዋ መውጪያና መግቢያ በሮች ላይ የጸጥታ ሀይሎች ተሳፋሪዎችን ከአዉቶቡሶችና ከግል መኪናዎች ዉስጥ በግድ ጎትተዉ እያወረዱ ጥብቅ ፍተሻ አንዳደረጉባቸዉ ለማወቅ ተችሏል። አዲስ አበባ ዉስጥ የሚገኙ አንዳንድ የፖለቲካ ተንታኞች ይህንን የወያኔ በድንገት የመጣ ፍተሻ ሰሜን ኢትዮጵያ ዉስጥ ከግዜ ወደ ግዜ እየተባባሰ ከመጣዉ የአማጽያን እንቅስቃሴ ጋር ሲያያይዙት ሌሎች ደግሞ በቅርቡ አዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ዉስጥ የደረሰዉን አይነት የቦምብ ፍንዳታ ከወዲሁ ለመከላለክ ነዉ ይላሉ፤ ሆኖም እንዚህ ወገኖች አገዛዙ ለምን ባህርዳር ላይ እንዳተኮረ የሰጡት ምንም አይነት ምክንያት የለም።


የጸጥታ ኃይሎቹ በሚያካሂዱት ፍተሻ ባህርዳርና አካባቢዋ ዉስጥ የመንግስትና የግሉ ዘርፍ ስራና ህዝባዊ እንቅስቃሴዎች የተስተጓጓሉ ሲሆን ህዝቡም በከፍተኛ ደረጃ እየተንገላታ መሆኑን የከተማዋ ነዋሪዎች በመናገር ላይ ይገኛሉ። የወያኔ አገዛዝ በህዝብ ላይ ለመፈጸም ለማያስባቸዉ ጭፍጨፋዎች ህጋዊ ሽፋን ለመስጠት እንዲህ አይነት እርምጃ መዉሰዱ የተለመደ ነዉ ያሉት አንድ ስማቸዉ እንዲገለጽ ያልፈለጉ ከፍተኛ የኢህአዴግ ባለስልጣን ይስ የሰሞኑ የባህርዳር ፍተሻ ሰሜን ኢትዮጵያ ዉስጥ አገዛዙን በማስጨነቅ ላይ ያለዉን የወጣቶች እንቅስቃሴ ለማፈንና አባላቱን ለመግደል የታቀደ እንደሆነ ገልጸዋል። ዊኪሊክስ የተባለዉ ሚስጢር አጋላጭ ድርጅት የዛሬ ሁለት አመት ይፋ ያደረገው መረጃ በግልጽ እንዳሳየዉ የአሜሪካ ኢምባሲ የኢትዮጵያ መንግስት በአገሪቱ የሽብር አደጋ አለ ለማስባል ሆን ብሎ ፍንዳታዎችን ያቀናብራል ብሎ እንደሚያምን መግለጹ ይታወሳል።


ይህ በእንዲህ እንዳለ በባህርዳር አንድ የባጃጅ ሹፌር በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድሎ ተገኝቷል። በወጣትነት እድሜ ክልል የሚገኘዉና የቀበሌ 7 ነዋሪ የሆነው ይህ ወጣት በከፍተኛ ሁኔታ የተደበደበ ከመሆኑም በላይ ሁለት አይኖቹ በአሳቃቂ ሁኔታ ወጥተዉ ከተጣለበት ቦታ ከሁለት ቀ አይኖቹ ወጥተው ከቀናት በሁዋን በኋላ ነው በፍለጋ የተገኘዉ። ኢሳት ሬድዮና ቴሌቪዥን በግድያዉ ዙሪያ የባሀርዳርን ፖሊስ ኮሚሽን ለማናገር ያደረገዉ ሙከራ እንዳልተሳካ ለማወቅ ተችሏል።
 G7 November 2, 2013

Monday, 4 November 2013

                   ሊበሏት የፈለጓትን አሞራ ይሏታል ጅግራ


ባለፈዉ ዐርብ መስከረም 25 ቀን 2006 ዓ.ም. የወያኔዉ ሎሌ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ አዲስ አበባ ዉስጥ ለአገር ዉስጥና ለዉጭ አገር ጋዜጠኞች በሰጠዉ ጋዜጣዊ መግለጫ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በየእሁዱ ለሚጠሩት ሰልፍ ጥበቃ ማድረግና በየእሁዱ ተመሳሳይ ጥያቄ ማድመጥ መንግስትን ከሚገባዉ በላይ ያሰለቸዉ ስለሆነ እነዚህ አንድ አይነት ጥያቄ ያነገቡ ሰልፎች የሚቀጥሉ ከሆነ የተቃዉሞ ሰልፍ ማድረግ ይከለከላል በማለት ጌቶቹና ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች የመብትና የነጻነት ጥያቄ የሚያነሳ ማንንም ሰዉ ለማሰር፤ ለመደብደብና ለመግደል ያላቸዉን እቅድ በግልጽ ተናግሯል። የሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄ ባቀረቡ ቁጥር መሪዎቻቸዉ የሚታሰሩባቸዉ፤ አባላቶቻቸዉ የሚደበደቡባቸዉና ቢሯቸዉ ተሰብሮ ንብረታቸዉ የሚዘረፍባቸዉ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ድርጅቶች አንድም ቀን ሰለቸን ሳይሉ ደብዳቢዉ፤ አሳሪዉና የተቃዋሚ ድርጅቶችን ቢሮ እየሰበረ ንብረታቸዉን የሚዘርፈዉ ወያኔ ሰላማዊ ሰልፍ “ሰለቸኝ” ማለቱ ወያኔ ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚደረግ ምንም አይነት ትግል የሱን የስልጣን “ዘለአለማዊነት” የሚጻረር መስሎ ከታየዉ ምንም ነገር ከማድረግ ወደ ኋላ የማይመለስ ፀረ ህዝብ ኃይል መሆኑን እንደገና አረጋግጧል።
ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከዚህ ቀደም ቤት ውስጥ ሆነው ይጠይቁት የነበረውን ጥያቄ አሁን አደባባይ ወጥተዉ መጠየቅ መቻላቸዉ ዲሞክራሲያዊ ስኬት ነው ያለዉ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ በሌላ በኩል ደግሞ ሰላማዊ ሰልፍ በችርቻሮ የሚሰጥ የወያኔ ችሮታ ይመስል ሰልፉ በየእሁዱ የሚቀጥል ከሆነ ሰልችቶናልና እንከለክላለን ማለቱ እንደ ግንቦት 7 እምነት ቀድሞዉንም ቢሆን ወያኔ ሰላማዊ ሠልፍ ማድረግ ይቻላል ብሎ ፈቃድ የሰጠዉ ለዲሞክራሲ ካለዉ እይታና እራሱ የጻፈዉን ህገ መንግስት ተከትሎ ሳይሆን እርዳታ ሰጪ ምዕራባዉያን አገሮችን ለማስደሰት ብቻ ነዉ።
አገር ዉስጥ የሚገኙ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከቅርብ ግዜ ወዲህ የተቀናጀ ትግል ማድረግ በመጀመራቸዉ ክፉኛ የተደናገጠዉ ወያኔ “ሊበሏት የፈለጓትን አሞራ ይሏታል ጅግራ” አንደሚባለዉ እነዚህን ኢትዮጵያ ዉስጥ ፍትህ፤ እኩልነትና፤ ዲሞክራሲ እንዲሰፍን የሚታገሉትን ፍጹም ህዝባዊና ፍጹም ሰላማዊ የሆኑ ድርጅቶች ለማጥፋት ሰበብ ሲፈልግ የተለመደዉን ግንቦት 7 የሚል ዘፈኑን መዝፈን ጀምሯል። የወያኔ አገዛዝ በአፉ አንደሚናገረዉ ለኢትዮጵያ ህዝብ የሚያስብና የሚጨነቅ ከሆነ ማድረግ ያለበት ከኢትዮጵያ ህዝብ ለሚቀርብለት ጥያቄ ተገቢዉን ምላሽ መስጠት ብቻ ነዉ። አለዚያ ህዝብ ጥያቄ ባነሳና ለመብቱና ለነጻነቱ በታገለ ቁጥር የሐይማኖት አክራሪዎች፤ የቀድሞ ስርዐት ናፋቂዎች ወይም የግንቦት ሰባት ተከታዮች ናችሁ እያለ ቢያቅራራ እንዲህ አይነቱ የተለመደ የአምባገነኖች ቀረርቱ ያ የማይቀረዉ ክፉ ቀን ሲመጣ ስንቅ እንደማይሆነዉና ከህዝባዊ ቁጣ እንደማያድነዉ ከወዲሁ ሊገነዘብ ይገባል። ደግሞም ግንቦት 7 አላማዉ፤ ለህዝብ ያለዉ ክብርና ለኢትዮጵያ አንድነት ያለዉ ቀናኢነትና የማያወላዉል አቋም በኢትዮጵያ ህዝብ ዘንድ በአጭር ግዜ ዉስጥ ከፍተኛ ተወዳጅነትን አስገኝቶለታልና የወያኔን የዕለት በዕለት አስተዋዋቂነት በፍጹም አይሻም።
ግንቦት 7 አላማዉና ፍላጎቱ እንደ ስሙ ፍትህ፤ ነጻነትና ዲሞክራሲ ነዉና የህዝባዊ ትግላችን አላማ ወያኔንና ዘረኛ ስርዐቱን መደምሰስ ብቻ ሳይሆን አገራችን ዉስጥ የህግ የበላይነት ሰፍኖ ኢትዮጵያ ዛሬም ነገም ከሽብርተኝነት የነጻች አገር አንድትሆን ነዉና ወያኔ ያሰኘሰዉን ቢናገር ወይም እንዳሰኘዉ ቢፎክር ንቅናቄያችን ከዚህ ህዝባዊ አላማዉ ንቅንቅ እንደማይል ለወገንም ለጠላትም ማረጋገጥ ይፈልጋል። ግንቦት 7 የኢትዮጵያና የህዝቦቿ ዋነኛ ጠላት ወያኔ ነዉ ብሎ ያምናል፤ ስለሆነም የግንቦት ሰባት ህዝባዊ ክንድ ያነጣጠረዉ በዚሁ በዋነኛዉ የህዝብና የአገር ጠላት ላይ ብቻ እንደሆነ ኢትዮጵያዉያንና ለኢትዮጵያ ህዝብ ሰላምና ብልጽግና የሚመኙ ሁሉ እንዲገነዘቡለት ይፈልጋል።
ግንቦት 7 ህዝባዊ አላማ አንግቦ፤ ግብ አስቀምጦና ወዳስቀመጠዉ ህዝባዊ ግብ የሚያደርሰዉን የትግል ስልት በጥንቃቄ ነድፎ የሚንቀሳቀስ ህዝባዊ እንቅስቃሴ ነዉ። ግንቦት 7 ወያኔና ዘረኛ ስርዐቱ ተደምስሰዉ ኢትዮጵያ በዜጎቿ ሙሉ ፍላጎትና ፈቃድ ብቻ የምትመራ አገር የመሆኗ ሀቅ የማይቀርና ምንም አይነት ምድራዊ ኃይል ገድቦ ሊያቆመዉ የማይችል ህዝባዊ ማዕበል ነዉ ብሎ ያምናል። ግንቦት 7 በዚህ አጋጣሚ በየዋህነት ተሳስተዉና ግዜያዊ ጥቅም አታሏቸዉ ከሚንቋቸዉና እንደ ቤት ዉስጥ ዕቃ ከሚጠቀሙባቸዉ ዘረኞች ጋር እጅና ጓንት የሆኑ እንደ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ አይነቶቹ የዋሆች የበደሉትን ህዝብ ይቅርታ ጠይቀዉ ህዝባዊ ትግሉን እንዲቀላቀሉ ወገናዊ ጥሪ ያቀርብላቸዋል። ከዚህ በተጨማሪ ግንቦት 7 ባለፉት ሁለት አመታት በተለይም ከወያኔዉ ቁንጮ ሞት በኋላ ከወያኔ ጋር ከፍተኛ ቅራኔ ዉስጥ የገባችሁ የኢህአዴግ አባል ድርጅቶችና በድርጅቶቹ ዉስጥ የምትገኙ የኢትዮጵያ ህዝብ ወገኖች ወያኔን ለማስወድ ከዛሬ የተሻለ ግዜ አይመጣምና ኑና በጋራ ጠላታችን ላይ እንዝመት የሚል ህዝባዊ ጥሪዉን ያስተላልፋል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!

  • facebook
  • google_buzz
  • twitter
  • rss
  • print
  • bookmark
  • email

Sunday, 3 November 2013

                         

                  የሚገነፍል ድስት የሚያበላሸዉ እራሱን ነዉ

የሚገነፍል ድስት የሚያበላሸዉ እራሱን ነዉ ግንቦት 7 መግለጫ በአለፉት ሁለትና ሦስት አመታት ዘረኞቹ የደደቢት ተዋንያን በተከታታይ ለህዘብ ካሳዩት ድራማና የኢትዮጵያ ህዝብም አይቶ እንዳላየ ታዝቦ ካለፋቸዉ የወያኔ ጉዶች ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ የህዝብ ትግል አቅጣጫ በቀየረና እምርታ በአሳየ ቁጥር የወያኔ ጀሌዎች ባልተባ ብዕራቸዉ እየጻፉና ባልተካነ ችሎታቸዉ እየከየኑ እንደቤት ዉስጥ እቃቸዉ በሚቆጣጠሩት የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ለህዝብ የሚያቀርቡት ሰዉ ሰዉ [...]


ለእንጀራየ ብዬ !!!

በሬ ሆይ በሬ ሆይ፤

ሞኙ በሬ ሆይ፤
ሳሩና አየህና ገደሉን ሳታይ፤
እልም ካለው ገደል ወደክብን ወይ።
ዛሬ ዛሬ “ለእንጀራየ ብየ ወይንኩ ለመኖር” የሚሉ አካሎች ቁጥር እና የአስተሳሰባቸው ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል።በተለይም ህግን እናስከብራለን ብለው የቆሙ አካሎች “ለእንጀራየ ብዬ ምንም ይሁን ምን የታዘዝኩትን ሳላቅማማ እፈጽማለሁ” የማለታቸው ነገር ከአሳሳቢ በላይም ነው።እነዚህ አካላት ዛሬ መረቅ የበዛበትን ወጥ በእንጀራ ለመጉርስ ሲሉ ነገና ተነገ ወዲያ የሚሆነውን ማየት ተስኗቸዋል። ዛሬ በያዙት ጠመንጃ ንጹሃን ዜጎችን ገድለው የሚበሉት እንጀራ ነገ ከማይወጡበት ገደል ውስጥ ሊከታቸው እንደሚችል ቆም ብለው ማሳብ ይኖርባቸዋል።
የህግ አስፈፃሚ አካላት ከእንጀራቸው በላይ የሚኖሩለት ትልቅ ቁምነገር ቢኖር የህግ የበላይነትን ማስከበር ነው። እነዚህ አካላት ከማንኛውም ተራ ዜጋ ተለይተው ህግን ለማስከበር ቃለ ማሃላ ፈፅመዋል። ይህን ቃለ መሃላ ሲፈጽሙ ዳኛው እና ተመልካቹ ሂሊናቸው ከፍ ሲል አምላክ ካላቸው አምላካቸው እንዲሁም ህዝብ ነው። ከዚህ ቃለ መሃላ በኋላ ህግ አስከባሪዎች በዋናነት የሚኖሩለትም ሆነ የሚሞቱለት ቁም ነገር እንጀራ ሳይሆን የህግ የበላይነት ነው። የምንኖርለትም ሆነ የምንሞትለት ዋናው ቁም ነገር የህግ የበላይነት እንጂ እንጀራ አይደለም ብለው የሚቆሙ የህግ አስከባሪዎች ባሉበት አገር ህግ ተከብሮ ዜጎች በሠላም ተረጋግተው ለመኖር እድሉን ያገኛሉ። ይህ ግን በኢትዮጵያችን እየሆነ አይደለም።
በኢትዮጵያችን የህግ አስከባሪዎች የሚኖሩለትም ሆነ የሚሞቱለት ዋናው ቁም ነገር “እንጀራዬ!” የሚባል ነገር ከሆነ ሃያ ሁለት ዓመት ሆነው።ህወሃት አገሪቷን ከተቆጣጠረ ዘመን ጀምሮ ኢትዮጵያችንን ድርና ማግ ሆነው እንደ አገር ሊያቆሟት የሚችሉ ዋና ዋና ክሮችን ሲበጣጥስ መኖሩ ከማንም የተሰወረ አይደለም። እየተበጣጠሱ ካሉ ክሮች መካከልም እውነትና ፍትህ ይገኙበታል። የህግ አስከባሪ አካላት ከፍትህና ከእውነት ይልቅ ለሚበላና ለሚጠጣ ከንቱ ነገር የበለጠ ትኩረት የሚሰጡ ሆነው እንዲያስቡ የተደረጉ ይመስላል። በዚህ በህወሃት ዘመን ህግን አስከብራለሁ ብሎ የማለ አካል “ለእንጅራ” ብሎ መሃላውን ያፈርስና ፍትህን ያጎድላል። ”ለእንጀራ”ብሎ በሃሰት ይከሰል ዳኛውም ያለ በቂ ማስረጃ ለእንጀራ ብሎ በሃሰት የእድሜ ልክ እስራት ይፈርዳል። በዚህም ዜጎች ይጎዳሉ ቤተሰብም ይፈርሳል።
ለእንጀራ ብሎ የገዛ ወገኑን የሚገድል ትውልድ መፈጠሩ አገሪቷን በእጅጉ የሚጎዳ ቢሆንም ህወሃቶች እንዲህ ያሉ ትውልዶችን መፍጠር በመቻላቸው ተሳክቶልናል ይላሉ ።በአንዲት አገር ውስጥ ፍትህ እና እውነት ከሚበላ ምናምን ነገር አንሳ ከተገኘች ያቺ አገር እንደ ባቢሎን ግንቦች ወድቃ ከመበታተን የሚጠብቃት ምንም ዓይነት ዋስትና የላትም።ኢትዮጵያ እንዲያ ነች። ኢትዮጵያ ውስጥ ነገን ተስፋ አድርጎ እና ተረጋግቶ ለመኖር የሚቻልበት ሁኔታ የለም። እንዲህም በመሆኑ ከሊቅ እስከ ደቂቅ የሚሰደድባት አገር ሁና የዓለምን ትኩረት ለመሳብ በቅታለች። ኢትዮጵያችን ከቄስ እስከ ዩንቨርስቲ ፕሮፌሰር፤ ከተማሪ እስከ ገበሬ፤ ከበረንዳ አዳሪው አንቱ እስከ ተባለ ባለ ሙያ ሁሉም በአንድ ላይ የሚሰደዱባት አገር ሁናለች።
ይሄ ለኢትዮጵያዊያን ትልቅ ውርደት ነው።ዘረኞቹ ህወሃቶችና በዙሪያው የተሰባሰቡ ዴማጎጎች ግን ይሄን ውረደት ለመረዳት አልቻሉም።
‹‹ወደ ኋላህ አትይ››

ካለፉት ዘመናት ይልቅ በዛሬው ዘመን የበዛው ኃጢአት ምንድነው? ብንባል ዝሙት፣ ሌብነት፣ ግድያ ብለን ልንጠቅስ፣ ይህንንም በቊጥር ስሌትና በመረጃ ልናቀርብ እንችላለን፡፡ ከእኛ ዕይታ የተሰወሩ፣ የዘወትር አቋማችንን የሚያነቃንቁ የተሰወሩ ስህተቶች አሉ፡፡ ነቢዩ፡- “ ስህተትን ማን ያስተውላል? ከተሰወረ ኃጢአት አንጻኝ” ያለው ለዚህ ነው (መዝ. 18÷12)፡፡ እነዚህ የተሰወሩ ኃጢአቶች ከሚፈጽማቸው ሰው ባሻገር ቆመው ያሉ አይደሉም፤ በውስጡ ያሉ፣ በኑሮው የሚገለጡ ኃጢአቶች ናቸው፡፡ ነገር ግን እንደሚገዙት እንኳ አያውቅም፡፡ በሚፈጽማቸውም ጊዜ የሕመም ስሜት የላቸውም፤ ስለለመዳቸውም ጽድቅ መስለው ይታዩታል፡፡ እነዚህን ኃጢአቶች ሰውዬው የሚኖርበት ማኅበረሰብ ስለተቀበላቸው የብዙኃን ውሸት እውነት መስሎ ታይቶት ሊሆን ይችላል፡፡ የቃሉና የቅዱስ መንፈስ ብርሃን የሚገልጣቸውን ስውር ኃጢአቶች ኅሊና ሊደርስባቸው አይችልም፡፡ ሰዎች መሳሳታቸውን የሚያውቁት ኅሊና የአደጋ ድምጽ ሲያሰማቸው ነው፡፡ ነገር ግን ኅሊና የተሰወረውን ስህተት ሁሉ የማወቅ አቅም የለውም፤ ኅሊና በኃጢአት ብዛትም ስለሚሞት የእውነት ሚዛን በመሆን ሁልጊዜ አያገለግልም፡፡ የኑሮአችን መመዘኛ ቃሉና ቅዱስ መንፈስ ብቻ ነው፡፡
          ኃጢአትን የምንፈጽመው መንፈሳዊ ዓይናችን ሲታወር ነው፡፡ ጭል ጭል የሚለውን ዕይታ ደግሞ ይበልጥ የሚያጨልመው በውስጣችን ያለው የተሰወረ ኃጢአት ነው፡፡ ነቢዩ፡- “ከተሰወረ ኃጢአት አንጻኝ” (መዝ.18÷12) አለ፡፡ የማላውቀውን ነገር ግን የማደርገውን ኃጢአቴን አስወግድልኝ ማለቱ ነው፡፡ መንጻት የሚያስፈልገው የቆሸሸ ነገር ነው፡፡ ነቢዩ፡- ‹ኃጢአት ያልመሰለኝ ነገር እያቆሸሸኝ ነውና ስም ጠቅሼ ከማልናዘዝበት ርኲሰት ንጹሕ አድርገኝ› በማለት ይጸልያል፡፡ እግዚአብሔር ራሱ ብቻ እንዳደረገልን የሚያውቀው ውለታ እንዳለ ሁሉ፤ እርሱ ብቻ እንዳደረግን የሚያውቀው ኃጢአት አለብን፡፡ የተገለጡ ኃጢአቶችን ያህል የተሰወሩ ኃጢአቶች ሰውን ያቆሽሻሉ፡፡ በቤት ውስጥ የት ቦታ እንዳለ የማይታወቅ ነገር ግን ቤቱን በክፉ ሽታ የሚያነቃንቅ ቆሻሻ አለ፡፡ ከተገለጠ ቆሻሻ ይልቅ የተሰወረ ቆሻሻ ለመወገድ ጊዜ ይፈጃል፡፡ ቶሎ አግኝቶ ማጽዳት ስለማይቻል ያውካል፡፡ የተሰወረ ኃጢአትም ከተገለጠ ኃጢአት ይልቅ ለመጽዳት ጊዜ ይፈጃል፡፡ የቃሉ ብርሃን ካልበራልን በቀር ልንደርስበት አንችልም፡፡ ታማሚዎች ሁሉ በሽታቸውን አያውቁትም፡፡ አንዳንዱ በሽታም ሕመም አልባ ሆኖ መጨረሻ ላይ ይገኛል፡፡ ሕመም ያለው በሽታ ቶሎ መፍትሔ ሲያገኝ የተሰወረውና ሕመም አልባ የሆነው በሽታ ግን ክፉኛ ይጎዳል፡፡ ሕመም አልባ የሆኑ የተሰወሩ ብዙ የድርጊት ኃጢአቶች አሉ፡፡ በአቋራጭ ጉዳይ ለማስፈጸም የሚከፈል ጉቦ ሰጪውም ሆነ ተቀባዩ መቼ ታመውበት ያውቃሉ? 

Saturday, 2 November 2013




ዘመነ አስተምህሮ



በቤተ ክርስተያናችን የዘመን አቆጣጠር /አከፋፈል/ መሠረት ከኀዳር 6 ጀምሮ እስከ ታኀሣሥ 13 ድረስ ያለው ወቅት ዘመነ አስተምህሮ ይባላል፡፡

መሀረ ማለት ይቅር አለ ማለት ሲሆን፤ ዘመነ አስተምህሮ ማለት ይቅርታ የመጠየቅ /የምልጃ/ ዘመን ማለት ነው፡፡ ዘመኑ ቤተ ክርስቲያን ስለ ልጆቿ ይቅርታ የምትጠይቅበት፤ ምዕመናንንም ስለ በደላቸው ይቅርታ የሚጠይቁበት፤ ስለዚህም በስፋት ትምህርት የሚሰጥበት ዘመን ነው፡፡
በዚህ ዘመን ያሉት አምስት እሑዶችና በእነዚህ እሑዶች የሚጀምሩት ሳምንታት አስተምህሮ፣ ቅድስት፣ ምኩራብ፣ መጻጉዕ፣ እና ደብረ ዘይት በመባል ይጠራሉ በየሳምንቱ ቤተ ክርስቲያን የምታቀርበውን ትምህርት በየጊዜው እናከብራለን የመጀመሪያውን ሳምንት /የአስተምህሮ/ ትምህርት እነሆ: -

እኛ የበደሉንን ይቅር እንደምንል፤ በደላችንን ይቅር በለን /ማቴ.6-12/

ይህ ቃል የተወሰደው ጌታችን በደቀ መዛሙርቱ በኩል እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ለሚኖሩ /ዛሬም ላለን/ ክርስቲያኖች እንዲህ ብላችሁ ጸልዩ ብሎ ካስተማረው ፀሎት ነው፤

በሰማይ የምትኖር አባታችን ሆይ ስምህ ይቀደስ መንግሥትህ ትምጣ ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን፤ የዕለት እንጀራችንን ዛሬ ስጠን፤ እኛም ደግሞ የበደሉንን ይቅር እንደምንል በደላችንን ይቅር በለን፤ ከክፉም አድነን እንጂ ወደ ፈተና አታግባን፤ መንግሥት ያንተ ናትና ኃይልም ክብርም ለዘለዓለም አሜን/ ማቴ.6. 9-14/

ይህ ጸሎት በጥንታውያን የቤተ ክርስቲያን አባቶች እና ሊቀውንት «የጌታ ጸሎት» ተብሎ ይጠራል፡፡ በእኛ ቤተ ክርስቲያን የጸሎቱን የመጀመሪያ ሐረግ በመያዝ «አባታችን ሆይ» ወይም በግእዝ «አቡነ ዘበሰማያት» እንለዋለን፡፡

ይህ ጸሎት ጌታችን ራሱ ያስተማረው በመሆኑ በቤተ ክርስቲያን ትልቅ ቦታ ይሰጠዋል፡፡ የሌሎች ጸሎታት ሁሉ ማሰሪያ /ማሳረጊያ/ ሆኖም ያገለግላል፡፡ በውስጡም «አባታችን ሆይ» ከምትለው ከመጀመሪያዋ ሀረግ ጀምሮ እስከ መጨረሻው ድረስ እጅግ ጥልቅ የሆኑና ነፍስን የሚያጠግቡ ወደ ሰማይ ከፍ የሚያደርጉ መንፈሳዊና ነገረ መለኮታዊ መልእክቶችን ያዘለ ነው፡፡

ይህ የዘመነ አስተምህሮ የመጀመሪያው ሳምንት ስለ ይቅርታ የሚሰበክበት ነውና በጸሎቱ ውስጥ ስለዚህ የሚናገረውን አንቀጽ መሠረት አድርገን እንማራለን፤

«እኛ የበደሉንን ይቅር እንደምንል በደላችንን ይቅር በለን» ከዚህ ቃል በርካታ ነገሮችን እንማራለን፤

1. እግዚአብሔር ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን እንደሚወድ

አምላካችን ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ባይወድ ኖሮ ይቅርታን እንድንጠይቅ አይነግረንም ነበር፡፡ አዎ እኛ ከተመለስን ምንም ያህል በደለኛ ብንሆን ይቅር ሊለን፤ ምንም ያህል ብንቆሽሸ ሊያድነን ዝግጁ ነው፡፡ እንዲህ እያለ ይጠራናል፤ «እናንተ ሸክማችሁ የከበዳችሁ፤ ወደ እኔ ኑ፤ እኔም አሳርፋችኋለሁ»፡፡ ስለዚህ በዚሀ ጸሎትም ላይ «በደላችንን ይቅር በለን» ብለን እንድንጠይቀው አስተማረን፤ ይቅር ይለን ዘንድ፡፡

2. ይቅር ለመባል ምን ማድረግ እንዳለብን፤

ይቅር ሊለን ስለ ወደደም ይቅርታን ለማግኘት ምን ማድረግ እንዳለብን በዚሁ ቃል ነግሮናል፤ ማድረግ ያለብን ምንድን ነው?
- ኀጢአታችንን ማወቅ፣ ማመን፣ ማስታወስ
- የበደሉንን ይቅር ማለት
- ይቅርታን መለመን

ኅጢአታችንን ማወቅ /ማመን/

ጌታ «በደላችንን ይቅር በለን» ብለን እንድንጸልይ ሲነግረን በመጀመሪያ ደረጃ በደለኛ እንደሆንን እያስታወስን /እንድናስታውስ እያደረገን/ ነው፡፡

ሁልጊዜም በማሰብ፣ በመናገርና በማድረግ የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ የሆነውን ልባችንን /ኅሊናችንን/ እና ሰውነታችንን እናቆሽሻለን፤ መድኃኔዓለም ክርስቶስ የሞተለትን ማንነታችንን እናጎድፋለን፡፡ ይህም የሰው ልጆች በቅድስና እርሱን መስለን እንድንኖር በኋላም የተዘጋጀልንን የዘለዓለም መንግሥት እንድወርስ ብቻ ፈቃዱ የሆነውን እግዚአብሔርን ያሳዝናል፤ በአርአያውና በአምሳሉ ለክብር የፈጠረው ሰውነታችን መጉደፍ ያስቆጣዋል፤ ንጹሐ ባሕርይ የሆነ እርሱ ኀጢአት አይስማማውምና፡፡

እንግዲህ ይቅር ለመባል በመጀመሪያ እንዲህ ኀጢአት እየሠራን መሆኑን ማወቅና ማመን ያስፈልገናል፡፡ ወደዚህ ዕውቀት ለመድረስም የቅዱሳት መጻሕፍትን ቃል መማር የግድ አስፈላጊ ነው፡፡ ምክንያቱም ስህተት የሚታወቀው ያለውን ሁኔታ /ድርጊታችንን ንግግራችንን፣ ሀሳባችንን.. / መሆን ከነበረበት /ከትክክለኛው/ ጋር በማነጻጸር በሚዛን ላይ በማስቀመጥ ነው፡፡ የማነጻጻሪያ ሚዛኖቻችን ደግሞ በቅዱሳት መጻሕፍት የተጻፉ ሕግጋትና ትዕዛዛት ናቸው፡፡ እነዚህን ስናውቅ ጉድለቶቻችን፣ ድካሞቻችን ፍንተው ብሎ ይታዩናል፡፡ አሊያ ግን እየበደለን ያልበደልን ሊመስለን ይችላል፡፡

የበደሉንን ይቅር ማለት