BRIGHT FUTURE FOR ETHIOPIANS !!!

BRIGHT FUTURE FOR ETHIOPIANS !!!

Saturday, 1 February 2014

እህትማማቾቹን ሕፃናት የደፈረው .....................................

ሁለት እህትማማቾች ሕፃናትን በማታለል ከወሰደ በኋላ የደፈራቸው ተከሳሽ በእስራት መቀጣቱን የፊንፊኔ ዙሪያ ኦሮሚያ ልዩ ዞን ፖሊስ አስታወቀ፡፡ በፊንፊኔ ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን ፖሊስ የወንጀል ምርመራና ፍትህ የማሰጠት የስራ ሂደት ሃላፊ ኮማንደር አበበ ተሾመ እንደገለፁት በሰበታ ሀዋስ ወረዳ ቦንዴ ዳባል ቀ/ገ/ማህበር ልዩ ስሙ ሞጆ ተብሎ የሚጠራው ነዋሪ የሆነው ሻምበል ያዳን ተባለው ላይ የእስራት ቅጣቱ ሊወሰንበት የቻለው ነሀሴ 4 ቀን 2005 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 በሚሆንበት ጊዜ የአጎቱን ሁለት ህፃናት ሴት ልጆችን አፋቸውን
በጨርቅ አፍኖ በመድፈሩ ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡...................

‹‹ከአገር እንድወጣ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶኛል›› አቶ አስመላሽ ሀዲሽ ወልዱ

‹‹ከአገር እንድወጣ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶኛል››  አቶ አስመላሽ ሀዲሽ ወልዱዋና ዜናተጻፈ በ  

የዛሬው ‹‹ምን እየሠሩ ነው?›› ዓምድ እንግዳችን አቶ አስመላሽ ሀዲሽ ወልዱ ይባላሉ፡፡ ተወልደው ያደጉት በትግራይ ክልል አጋሜ አውራጃ አዲግራት ከተማ ውስጥ ነው፡፡
ትምህርታቸውን እስከ ዘጠነኛ ክፍል በተወለዱበት አዲግራት ከተማ ተከታትለው፣ ወደ አሰብ ራስ ገዝ በመጓዝ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቀዋል፡፡ የደርግ መንግሥት መውደቅን ተከትሎ በ1983 ዓ.ም. ወደ አዲስ አበባ ከተማ መምጣታቸውን የሚናገሩት አቶ አስመላሽ በንግድ ሥራ ተሰማርተው ስኬታማ ሥራ እየሠሩ የነበሩ ቢሆንም፣ ባልታሰበ ድንገተኛ ገጠመኝ ከፍተኛ ችግር ውስጥ መውደቃቸውን ተናግረዋል፡፡ ስለገጠማቸው አስቸጋሪ የሕይወት ፈተናና አሁን ስላሉበት ሁኔታ ታምሩ ጽጌአነጋግሯቸዋል፡፡
ሪፖርተር፡- ወደ አዲስ አበባ የመጡት መቼ ነው?
አቶ አስመላሽ፡- በ1983 ዓ.ም. ነው የመጣሁት፡፡ 
ሪፖርተር፡- አዲስ አበባ ከመጡ በኋላ የተሰማሩበት የሥራ መስክ ምን ነበር?
አቶ አስመላሽ፡- አዲስ አበባ ከመጣሁ በኋላ የአስመጭና ላኪነት ፈቃድ በማውጣት በንግድ ሥራ ተሰማራሁ፡፡
ሪፖርተር፡- ምን ዓይነት የንግድ ሥራዎችን ነበር የሚያስመጡትና የሚልኩት?
አቶ አስመላሽ፡- የማስመጣው ጨርቃ ጨርቆችንና የምግብ ሸቀጣ ሸቀጦችን ነበር፡፡ ይኸንን የንግድ ሥራ ስሠራ በመንግሥት በኩል የሚጠበቅብኝን ግብርም ሆነ ሌሎች የንግድ ሥራው የሚጠይቀውን ግዴታዎች እየተወጣሁ ነበር፡፡ 
ሪፖርተር፡- በዚህ የንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩት እስከመቼ ነበር?
አቶ አስመላሽ፡- ከ1984 ዓ.ም. እስከ 1991 ዓ.ም. ድረስ ሠርቻለሁ፡፡ ከ1991 ዓ.ም. በኋላ ወደሌላ ሥራ ተዘዋወርኩ፡፡
ሪፖርተር፡- ምን ዓይነት ሥራ ለወጡ?..................

ኢህአዴግ ሚኒስትሮቹን የግንባሩን ስራ እንዲያከናውኑ መደበ

ጥር ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ ፓርቲውን እንዲመሩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን እና ሌሎች ሁለት ሚኒስትር ዴኤታዎችን ባለፉት ወራት መሾሙን ውስጥ አዋቂ ምንጮች ጠቆሙ፡፡

ኢህአዴግ የመንግስት መዋቅርን ከፓርቲው መዋቅር ጋር አደበላልቆ በመስራት ላይ እንደሚገኝ ተደጋጋሚ ወቀሳዎችና ትችቶች እየቀረቡበት የቆየ ሲሆን በዚህ መልኩ ግልጽ የሆነ አደረጃጀት በመያዝ የመንግስት ከፍተኛ አመራሮችን ሲመድብ ከአቶ መለስ ሞት በሃላ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ተብሎአል፡፡
ቀደም ሲል የግንባሩ ሊቀመንበርና ምክትል ሊቀመናብርት የግንባሩንና የአባል ፓርቲዎችን የሚመሩበት ሁኔታ የተለመደ ሲሆን የአሁኑ አደረጃጀት ግን ለየት የሚያደርገው በሚኒስትር ዴኤታ ማእረግ ጭምር በመንግስት ሃላፊነት ላይ የተመደቡ ሹማምንት ከነጥቅሞቻቸው ወደ ፓርቲው ሃላፊነት ተመድበው የመምጣታቸው ጉዳይ ነው፡፡ ሰዎቹ አብዛኛውን ጊዜያቸውን በፓርቲው ስራዎች እንደሚያጠፉ የጠቆሙት ምንጮቻችን ይህም ከመጪው ምርጫ ጋር በቀጥታ የተያዘ ነው፡፡..............

የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት ከሃገር ፈረጠጡ




(ዘ-ሐበሻ) ራሳቸው በጠሩት ግምገማ፣ ራሳቸውን አስገምግመው ከፓርቲው ሊቀመንበርነታቸው መነሳታቸው የንጽህናቸው ውጤት መሆኑን ሲናገሩ እንደነበረ የሚነገርላቸውና በአንድ ወቅት በጋምቤላ ስለነበረው ጭፍጨፋ ተጠያቂ ነህ ሲባሉ “መሳሪያውን ያቀበለው መለስ ዜናዊም መጠየቅ አለበት” ብለዋል የተባሉት የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንትና የአሁኑ የፌዴል ጉዳዮች ሚ/ር ደኤታ አቶ ኦሞት ኦባንግ ከሃገር መፈርጠጣቸው ተሰማ።

በስልጣን ዘመናቸው ፕሬዚዳንቱ የክልሉን ደን እያስጨፈጨፈና ህዝቡን እያፈናቀለ ስላለው የመሬት ሽያጭና ነጠቃ የክልሉ እጅ የለበትም በሚል የተናገሩት ኦሞት ሂይውማን ራይትስ ዎች ባወጣው ሪፖርት ላይ በክልሉ ስለሚካሄደው የመሬት ነጠቃ አቶ በረከት ስምኦን በበኩላቸው ምላሽ ሲሰጡ በክልሉ ከሶስት ሚሊዮን ሄክታር በላይ ባለቤት የሌለው መሬት መኖሩን መናገራቸው አይዘነጋም።........

ልፋ ያለው በሕልሙ ዳውላ ይሸከማል! ጠርናፊና ተጠርናፊ (ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም )

መስፍን ወልደ ማርያም
ጥር 2006
ሰሞኑን እንደአዲስ ሆኖ የሚወራው ስለጥርነፋ ነው፤ ጥርነፋ ከዲያብሎስ ፋብሪካ የወጣ የክፋትና የጭቆና መሣሪያ ነው፤ ሰዎችን በመጨቆንና በማሰቃየት፣ ምቾትና እንቅልፍ በማሳጣት፣ ፍርሃትንና ስጋትን በማሰራጨት ሕዝብን ለጥ-ጸጥ አድርጎ ለመግዛት የሚፈልጉ ጠርናፊዎች፣ አምባ-ገነኖች፣ ጨቋኞች፣ አፋኞች፣ ዘራፊዎች፣ ወሮበሎች፣ ምድራዊም ሆነ ሰማያዊ ሕግ የማይገዛቸው፣ አምላካቸው አድርገው የሚያገለግሏቸው ሎሌዎችን በሆዳቸው ገዝተው የሚያሰልፉ ናቸው፤ እንኳን የገጠር ልጆችና አኛም የአዲስ አበባዎቹ መሰንከል ምን እንደሆነ እናውቃለን፤ እንስሳትን (በቅሎዎችንና አህዮችን፣ አንዳንዴ በገግና ፍየልም) የፊት እግር ከኋላ እግር ጋር በአጭር ገመድ እያሰሩ እንደልባቸው እንዳይንቀሳቀሱ ማድረግ ነው፤ ሀብት በመሆናቸው ቢጠፉ ባለቤቶቹ ይጎዳሉ፤ ስለዚህ በየአካባቢያቸው ያለውን እየጋጡ ችለው እንዲኖሩ ለማድረግ ቀላሉ ዘዴ መሰንከል ነው፡፡
Prof. Mesfin Woldemariam : is an Ethiopian Human Rights activist and philosopher
ለሰውም ቢሆን ዓላማውም ዘዴውም አንድ ነው፤ ልዩነቱ የሰው ልጅ እንቅስቃሴው አካላዊ ብቻ ሳይሆን አእምሮም መንፈስም ስላለው መሰንከሉ አካላዊ ብቻ አይሆንም፤ እንዳያስብ አእምሮውን ማፈን ግዴታ ይሆናል፤ ለአምባ ገነኖች ችግር የሚመጣው የሰዎች አእምሮ ሲያስብ ነው፤ ያሰበውንም መናገርና መጻፍ ሲጀምር ነው፤ ‹‹መጥፎ ሀሰብ››፣ ማለትም ለጨቋኞቹ የማይበጅ ጥሩ ሀሳብ በንግግር፣ በጽሑፍ፣ በራድዮና በቴሌቪዥን ቢተላላፍና ብዙ ሰዎች ቢሰሙት አገር ይረበሻል፤ ሰው ሁሉ ሽብርተኛ ይሆናል፤ አገዛዙ ሕዝቡን ለመሰንከል ብዙ ዘዴዎች አሉት፤ በስም ማጥፋት እንዳልከሰስ ዘዴዎቹን አልናገርም፤ ነገር ግነ ክፉ እንቅልፍ ይዞት የሄደ..............

ኢትዮጵያዊያን አንድ ሆነን ለነፃነት መታገል ያስፈልጋል!!!

ቃልኪዳን ካሳሁን (ከኖርዌ)

እንደሚታወቀው ኢትዮጵያዊያን በመላው አለም እንደሚኖሩ ይታውቃል። ከኦሮሚያ ይሁን ከአማራ፣ ከሶማሌ፣ ከደቡብ ፣ አፋር፣ ትግራይ፣ ቤኒሻንጉል፣ ድሬ . . . . . . .. ብቻ ከየትም ይምጡ የሁሉም ኢትዮጵያዊ የስደት መንሾ “በፖለቲካ አልያም የተሻለ ህይወት ፍለጋ” ከመሆን አይዘልም።
(በሀገሩ መኖር ማን ይጠላል . . . . . . . )Kalikidan
ብዙ ጊዜ የማስበው ታዲያ ኢትዮጵያውያኑ በሰው ሀገር ሲኖሩ እንዳውም ከሀገር ውስጥ የበለጠ አንድንትና መግባባት ወይም አብሮ የመኖር ስሜት ይኖራቸዋል። በሰው ሀገር የመኖርን የህይወት ትግል ለመላመድና ለማሸነፍም ከሀገር ልጅ የበለጠ አለኝታ፣ አይዞህ/ሽ ባይ እና አጋዥ የለምና። በተለያዩ አጋጣሚዎች የምንሰማው ግን ከዚህ በተቃራኒው የሆኑ እውነታዎችን ነው። በጥርጣሬ መተያየት፣ የብሄርና የፖለቲካ ክፍፍል………ሌላም ሌላም።
እርግጥ ነው ሁላችንም አንድ አይነት አቋም ሊኖረን አይችልም፡........

የአማራው ክልል መሪ በአማራው ህዝብ ላይ ተሳለቁ


ጥር ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአማራ ክልል ም/ ፕሬዚዳንት እና የብአዴን ጽ/ቤት ሃላፊ የሆኑት አቶ 


አለምነው መኮንን “የአማራው ህዝብ ሰንፋጭ የሆነ ትምክተኝነት የተጠናወተው በመሆኑ በቤንሻንጉልና በሌሎችም ቦታዎች 


ለመሰደዱ ምክንያት ሆኖታል” በማለት፣ ለብአዴን ነባርና አዳዲስ ካድሬዎች ተናግረዋል።


ካድሬዎቹ “የአማራው ህዝብ ለምን ይሰደዳል? ለምን በእየክልሉ ጥቃት ይደርስበታል? አማራውን ከጥቃት ለመከላከል ለምን ሙከራ አይደረግም 

በማለት ጥያቄ ያቀረቡ ሲሆን፣ ም/ል ፕሬዚዳንቱ የአማራው ህዝብ በቅድሚያ እንዳይሰደድ ለማድረግ ስራ እየተሰራ ነው፣ ነገር ግን ከተሰደደ 

በሁዋላም ቢሆንም ሰንፋጭ የሆነውን ትምክህተኝነቱን በመተው ከሌላው ጋር ለመኖር መልመድ አለበት ብለዋል።

አማራው “በባዶ እግሩ እየሄደ የሚናገረው ንግግር ግን መርዝ ነው” ያሉት ምክትል አስተዳዳሪውና የብአዴን የጽህፈት ቤት ሃላፊው፣ ይሄ መርዝ 

ንግግሩ አንድ የሚያደርግ አይደለም ሲሉ አክለዋል።................