BRIGHT FUTURE FOR ETHIOPIANS !!!

BRIGHT FUTURE FOR ETHIOPIANS !!!

Friday, 6 March 2015

ማስተርስ/ዶክተሬት እንደ መለዋወጫ እቃ!

ታሪኩ አባዳማ
ልጄ አስራ ሁለተኛ ክፍል ስለጨረሰ የደስታዬ ተካፋይ ትሆኑ ዘንድ… የሚል ግብዣ ደርሷችሁ አያውቅም? እናንተም ፋሽኮ ቪኖ ወይንም እናትና ልጅ አረቄ ይዛችሁ ድግሱን ለማድመቅ ሳትሄዱ አልቀራችሁም – የዚያን ዕለት ጎረምሶቹ የቀለጠ ፓርቲ ደግሰው እስኪነጋ ይጨፍራሉ አሉ… ይህስ ይሁን።
ድህረ ምረቃ ፕሮግራም ላይ መሆኑን አንድም ቀን ሲናገር ሰምታችሁ የማታውቁት በቅርብ የምታውቁት ሰው ፣ እንዲያውም በመደበኛ ትምህርት ከስንተኛ ክፍል ነበር? አቋርጦ ወደ ሄደበት ሄዶ (ጫካ ወይንም ምርኮ) ግን የዛሬ ‘ሹም’ ‘የማስተርስ ፣ ዶክትሬት ዲግሬዬ በፖሰታ ስለደረሰኝ የደስታዬ ተካፋይ እንድትሆን ብሎ ቢጠራችሁስ? ይኼ ሰው ድሮ ትምህርት ቤት የተመዘገበበት ስም ሌላ ነበር… አሁን ደግሞ አዲስ ስም ብቻ ሳይሆን አዲስ ማዕረግ ፣ አዲስ ቤት ፣ አዲስ መኪና… ምኑ ቅጡ… ባናቱ ላይ ዲግሪ ሸምቶበታል።

Wednesday, 4 March 2015

በሱዳናዊው የመኪና አሽከርካሪ ጥቃት የደረሰባት ኢትዮጵያዊት አረፈች

የካቲት ፳፭(ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የካቲት 24 ፣ 2007 ዓም በሱዳናዊ ሹፌር በአሰቃቂ ሁኔታ ጥቃት የተፈጸመባት ኢትዮጵያዊት ወጣት ማረፉዋን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል። ወጣቷ በአሰቃቂ ሁኔታ በጩቤ ተወጋግታ መሞቱዋን የገለጹት የወረታ ነዋሪዎች፣ ሹፌሩ በቁጥጥር ስር ውሎአል ቢባልም በትክክል ስላለበት ሁኔታ ማወቅ እንዳልቻሉ ገልጸዋል።

ካህኑ የአረና አባል በመሆናቸው ዘግናኝ ድብደባ ተፈጸመባቸው

የካቲት ፳፭(ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የቀፍታ ሑመራ ወረዳ  በረኸት  ከተማ  ነዋሪ የሆኑት ቄስ ሕሉፍ ኸሕሳይ የዓረና-መድረክ ኣባል በመሆናቸው ብቻ ዘግናኝ ድብደባ እንደተፈጸመባቸው ከፓርቲው ጽህፈት ቤት የወጣ መረጃ አመለከተ።
እንደ መረጃው ከሆነ  ቄስ ህሉፍ  በደረሰባቸው ዘግናኝ ድብደባ  በህይወትና በሞት መካከል የሚገኙ ሲሆን፤ ለድብኢደባቸው ምክንያቱ  የአረና አባል መሆናቸው ብቻ ነው። የካቲት 17 ቀን 2007ዓመተ ምህረት  ምሽት 1፡00 ሰዓት ኣከባቢ  በሶስት ታጣቂዎች ከለላነት ተደብቆ የነበረ  ሰው በድንጋይ ደጋግሞ በመደብደብ ለከፋ ኣደጋ እንደዳረጋቸው  ፓርቲው ጠቅሷል።

Tuesday, 3 March 2015

ሰማያዊ ፓርቲ የቅስቀሳ መልእክቱን እንዲለውጥ ተጠየቀ።

የካቲት ፳፬(ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ ፣ ኤፍ ኤም 96.3፣ ሰማያዊ ፓርቲ ለምርጫ ቅስቀሳ ያቀረባቸውን መልእክቶች እንዲለውጥ፣ ካልለወጠ ግን እንደማያስተላልፍ ገለጸ።
ጣቢያው እንዲወጡ ከጠየቃቸው መልእክቶች መካከል ‹‹ሀገራችን ዛሬ በቀሪው ዓለም የምትታወቀው በእርስ በርስ ጦርነት ነው›› የሚለው የሚገኝበት ሲሆን፣ መልእክቱ ለአመጽና ለሁከት የሚያጋልጥ ነው የሚል ምክንያት አቅርቧል።

Tedros Adhanom caught in $20 million teen prize scandal

Tedros Adhanom
Government of Australia and Rotary Foundation deny funding teenager 
By Abebe Gellaw 

Tedros Adhanom

ADDIS VOICE - The Foreign Minister of Ethiopia has been caught in an explosive web of lies with a schoolgirl as the Government of Australia and the Rotary Foundation have denied giving 20 million Australian dollars to a 14-year old teenager, whom the nation’s “top diplomat” publicly praised and endorsed as an “exemplary philanthropist” and claimed her to be the winner of an unnamed “international prize”.

Monday, 2 March 2015

A Magna Carta for Ethiopia?

By Alemayehu G Mariam 
March 2, 2015

I am celebrating the 800th anniversary of the Magna Carta Libertatum or the Great Charter of English Liberties. Whoa! Hold it! I understand your question!
Why is a guy born in Africa (Ethiopia) now living in America celebrating a document written by a bunch of disgruntled and rebellious English barons quarrelling with a feudal monarch over taxes and restoration of their feudal privileges in Medieval England 800 years ago?

የአድዋ ድል በአል ተከበረ!

የካቲት ፳፫(ሃያሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢትዮጵያውያን የጣሊያንን ወራሪ ሃይል ድል የመቱበትና ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቁሮች በነጮች ላይ የአሸናፊነት ታሪክ የጻፉበት የአድዋ ድል 119 አመት በአል በአዲስ አበባ ተከብሮአል።