
ይህ ዜና እስከ ተጠናከረበት ግዜ ድረስ የወጣቷ ሬሳ አለመንሳቱን የሚናገሩ ምንጮች በአካባቢው የፓስፖርተ እድሳት እና መስል ተዘማጅ ጉዳዩቹን ለማስፈጸም የቆንስላ ግቢውን አጨናነቀው እምባ ሲራጭ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ከቆንስላው ጽ/ቤት እንዲወጡ መደረጋቸውን የአይን እማኞቹ አክለው ገልጸዋል ። ይህ በዚህ እንዳለ የሬሳ ጉዳይ የሚከታተለው እና የቀድሞ የኮሚኒቲ አመራር አቶ መሃመድ ሸህ ተፈቅዶለት ወደ ግቢው ሲገባ ያዩ ምንጮች ቦታው ላይ የሳውዲ ፖሊሶች እና ዲፕሎማቶች መገኘታቸውን አረጋግጠዋል ። የጅዳ ቆንስ ጽ/ቤት የእህቶቻችንን አስከሬን ሲያስተናገድ የመጀመሪያ ግዜው እንዳለሆነ የሚናገሩ ወገኖች በዲፕሎማቱ የአሰራር ድክመት በአንድ ወር ውስጥ ብቻ ለሁለተኛ ግዜ ታንቃ ህይወቷ ባለፈው ወጣት ተደናግጠው ሲጮጮሁ በነበሩ ኢትዮጵያውያን የቆንስላው ጽ/ቤት ድባብ ወደ መቃብር ስፍራ ነት ተለውጦ ማምሸቱን ይናገራሉ ።
በአሁኑ ግዜ በዚህ የቆንስላ ቅጥር ግቢውስጥ ከ 40 የሚበልጡ ተፈናቃይ የኮንተራት ሰራተኞች ከሰው እይታ ተገለው ይሚገኙ ሲሆን ባዶ ክፍሉ ውስጥ ያለምንም እርዳታ ሃገር ትገባላቹ በሚል ተስፋ መጋዘን ተቆልፎባቸው ለበለጠ ስቃይ እና መከራ እይተዳረጉ ከሚገኙ እህቶቻን መሃከል አብዛኛዎቹ የፈላ ውሃ በአሰሪዎቻቸው የተደፋባቸው የተድፈሩ እና ደሞዛቸው የተነጠቀ መሆኑ ይነገራል።፡፤ የወገኖቻችን ሞት ከሚፈበረከበት ሁለተኛው ማዕከል ጅዳ ከሆነው የ ቆንስላ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ በአንድ ወቅት አንድ የውሃ ጉድ ጓድ ውስጥ ሬሳዎ በተገኘ ኢትዮጵያዊት ጉዳይ የህ.ወ.ህ.ቱ አባል አቶ ገሬ ለወራት ወህኒ ቢወርዱም የሞቾ ምስኪን ጉዳይ ተድበስብሷ ሲቀር አቶ ገሬ ከወራት እስራት በኋላ በወጭ ጉዳይ ግፊት መፈታታቸው በህዝብ ዘንድ ተቃውሞ ማስነሳቱ አይዘነጋም።
Ethiopian Hagere ጅዳ በዋዲ
No comments:
Post a Comment