
ባለፈው ሳምንት ፍርድ ቤት ቀርበው የዋስትና መብታቸው ሳይከበር ወደ እስር ቤት የተመለሱት የታክሲ ሹፌሮች ከሰማያዊ ፓርቲ የመጣ ትእዛዝ ነው የስራ ማቆም አድማ ያደረጋችሁት በሚል ጉዳዩን ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር በሃሰት ለማገናኘት በፖሊሶች በሃይል ለማሳመን ጥረት ቢደረግም እንዳልተሳካ ምንጮቹ ገልጸው እስካሁን ምንም አይነት መረጃም ሆነ ማስረጃ መርማሪዎች በማጣታቸው በስራ ማቆም አድማ ላይ የተሳተፉ የታክሲ ሹፌሮችን በታሰሩት ላይ እንዲመሰክሩ በጥቅም እያግባቧቸው መሆኑን ምንጮቹ ገልጸዋል::
በአድማው ወቅት የታክሲ ባለንብረቶችም የታሪፍ ማስተካከያ አለመደረጉን በመቃወም የታክሲ ሹፌሮቹን ተቀላቅለው የነበር ሲሆን የጎንደር ከተማ አስተዳደር ባለስልጣናት ሾፌሮቹና ባለንብረቶቹ ወኪል ልከው እንዲነጋገሩ በጊኤው የጠየቁ ቢሆንም ሹፌሮቹ “የክልሉ መንግስት ወከሎችን በተደጋጋሚ የማሰር ልምድ ስላለው ወኪል አንልክም” ብለው እንደነበር ይታወሳል::
No comments:
Post a Comment